“ኤርትራም ወደ እናት ሀገሯ ትመለሳለች”
ለአምላክ የቀረቡ ቅዱሳንና ንጹሃን ሰዎች ወደፊት ገና እነሱ ያልኖሩበት ዘመን ሁኔታ አስቀድመው የማወቅ ጸጋ ስለሚሰጣቸው ” እንዲህ ይሆናል: ይሄ ይመጣል ይሄ ይሄዳል ” እያሉ ይናገራሉ :: እነዚህ ቅዱሳን የሚናገሩት እውነት ትንቢት ሲባል እነሱ ተናጋሪዎቹ ደግሞ ነብያት ይባላሉ:: የሚመጣውም ትውልድ አንብቦ ወደፊት ለሚሆነው ነገር ይዘጋጅ ዘንድም የትንቢት መጽሐፍት ይጽፋሉ:: ለምሳሌ በመጽሓፍ ቅዱስ ከትንቢተ ኢሳይያስ ጀምሮ ያሉት የትንቢት መጻሕፍቶች በሙሉ በየግዜው የሚከሰተውን ነገር አስቀድመው የሚናገሩ መጻሕፍት ናቸው::
በሀገራችንም በርካታ ቅዱሳን በሀገርም ላይ ሆነ በግለሰቦች ላይ ስለሚከሰት ጉዳይ : በርካታ ትንቢቶችን ተናግረዋል:: በተለይ በሀገር ዙርያ ትንቢት የተናገሩ ብዙ አባቶችን መጥቀስ ይቻላል:: የወሊሶው አባ ወልደ ትንሳኤ( በኋላ አቡነ ዴዎስቆሮስ) የታወቁ አጥማቂ ነበሩ:: አጋንንቱን እየገዘቱ ያናዝዙት ነበር:: እሳቸውም የሚናገሩት ትንቢት መሬት ወድቆ አያውቅም ነበር::የመቄቱ አባ አዳነ ካሳውም ይሄ ጸጋ የተሰጣቸው ልዩ አባት መሆናቸውን የሚያውቃቸው ያየና እሳቸውን የሚሉትን የሰማ ብቻ ነው::
እኔ በእድሜዬ ባህታዊ ገብረመስቀልን አስታውሳለሁ:: በ1980ዎቹ መጀመርያ ” ትልቁ ዘንዶ አራት ኪሎ ላይ ወደቀ:: የሱን ደም የነኩትም በሙሉ እፍረት ገጠማቸው”…
View original post 897 more words